የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳንት በዓለም አቀፍ ደረጃ ስለሚገኝ  የስራ አጦች ቁጥር መጨመር ለጨፌ ያቀረቡት የተሳሳተ መረጃ

The speech made by Oromia regions president Shimelis Abdisa about the increase in unemployment rate in the world is incorrect

ሐምሌ 05፣ 2015

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳንት ሽመልስ አብዲሳ እንደ ክልልም ሆነ እንደ ሀገር ከገጠሙ ችግሮች መካከል አንዱ ስራአጥነት መሆኑን ከትላንት በስቲያ ሐምሌ 03/2015 ከጨፌ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ በሰጡበት ወቅት ጠቅሰው ነበር።

ችግሩ በተለያዩ የዓለም ሀገራትም ፈተና መሆኑን የተናገሩት ፕሬዘዳንቱ የስራ አጦች ቁጥር በዓለም አቀፍ ደረጃ16% በላይ ማደጉን ተናግረዋል።

ይህ ንግግራቸዉም በዚህ የኦ ኤን ቀጥታ ስርጭት ማስፈንጠሪያ 2:36:45 ጀምሮ ይገኛል፡ https://fb.watch/lJqqMYbnKz/?mibextid=v7YzmG

በተጨማሪም በደቡብ አፍሪካ እና ናይጄሪያ ዉስጥ ያለዉን የስራ አጥነት ችግር በማንሳትበደቡብ አፍሪካ የስራ አጦች ቁጥር 60% አድጓል፣ በናይጄሪያ ብቻ 53% አድጓልብለዋል። በተመሳሳይ በቻይናም የስራ አጦች ቁጥር 20% ማደጉን ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ ፕሬዘዳንቱ ያቀረቧቸው መረጃዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ በጉዳዩ ተአማኒ መረጃዎችን በማቅረብ ከሚታወቁ ተቋማት መረጃ ጋር የሚጣጣም እንዳልሆነ ተመልክተናል።

የዓለም ባንክ መረጃ እንደሚያሳየው ዓለም አቀፍ የስራ አጦች ብዛት 2019 5.5% ነበር። 2020 6̈.9% 2021 6.2% እና 2022 5.8% እንደሆነ ያሳያል: https://data.worldbank.org/indicator/SL.UEM.TOTL.ZS

የዓለም አቀፍ የስራ ድርጅት ILO 2023 ግምትም 5.8% ነው፡ https://ilostat.ilo.org/data/#

በዚሁ መሰረት የሁለቱ በዓለም አቀፍ  ደረጃ የስራ አጦች ቁጥር 16% በላይ ማደጉን የሁለቱ ተቋማት መረጃዎች አያሳዩም።

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት IMF መረጃ እንደሚያሳየው 2020 በደቡብ አፍሪካ የነበረው የስራ አጦች ቁጥር29.2% ሲሆን 2021 ወደ 34.3% ከፍ ብሎ ነበር።

2022 ደግሞ 33.5% የነበረ ሲሆን 2023 ግምትም  34.7% ነው፡https://www.imf.org/external/datamapper/LUR@WEO/WEOWORLD/ZAF

ይህ የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት መረጃም የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳንት ሽመልስ አብዲሳ እንደተናገሩት በሀገሪቱ የስራ አጦች ቁጥር 60% ማደጉን ወይም መጨመሩን አያሳይም።

በተመሳሳይ ሁኔታ ባለፉት ሶስት ዓመታት የቻይና የስራ አጥ ዜጎች ምጣኔ ከፍተኛው 4.2 % ሲሆን ዝቅተኛውደግሞ 4% ነው።

ይህም የቻይና የስራ አጥ ዜጎች ቁጥር በፕሬዘዳንቱ በተገለጸው ደረጃ 20% እንደተጠቀሰው ያለማደጉን የሚያመላክት ነው፡https://www.imf.org/external/datamapper/LUR@WEO/OEMDC/ADVEC/WEOWORLD/CHN

ወቅታዊ መረጃዎችን ቀጥታ በኢሜልዎ ለማግኘት ይመዝገቡ

    ያቀረቡትን የግል መረጃ በግላዊ መመሪያችን መሠረት እንጠብቃለን::