የኤርትራው ፕሬዝደንት ሰጡት ተብሎ የተሰራጨ ሀሰተኛ መግለጫ
ሚያዝያ 02፣ 2015
“Wolkayt Tgedie Amhara Revolutio# ወልቃይትጠገዴ የአማራ ንቅናቄ” የሚል ስያሜ ያለው የትዊተርአካውንት በትናንትናው እለት አንድ አነጋጋሪ መረጃ አጋርቶ ነበር።
ይህ ከ5,400 በላይ ተከታታዮች ያሉት አካውንት “ታላቅ ሰበር ዜና” በሚል መረጃውን ይጀምርና “የኤርትራውፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቅ የአማራ ልዩ ኃይልን መፍረስ የለበትም ሲሉ በ ERI TV መግለጫ ሰጥተዋል” የሚልመረጃ አጋርቷል።
አክሎም “በመግለጫቸው ከአማራ ልዩ ኃይልና ሕዝብ ጎን መሆናቸውንና አስፈላጊውን የሎጅስቲክ ድጋፍእንደሚያደርጉ አስታውቀዋል” ይላል ይህ አሁን ላይ 520 መውደድ (like) እና 204 መልሶ ማጋራት (retweet) የተደረገ መረጃ።
ይህን መረጃ በመውሰድ (ኮፒ በማድረግ) እንደ Dessie Press፣ Tana Media Network፣ ወሎ ሚድያ ሴንተር(WMC)፣ ፩ አማራ… ወዘተ ያሉ የፌስቡክ ገፆች እና አካውንቶችም መረጃውን በስፋት አጋርተዋል።
ይህን መረጃ ተንተርሶ ኢትዮጵያ ቼክ ባደረገው ማጣራት የኤርትራው ፕሬዝደንት ምንም አይነት ንግግር በዚህዙርያ በኤርትራ ቴሌቭዥን (Eri TV) ላይም ሆነ በሌሎች ሚድያዎች እንዳላደረጉ መመልከት ችለናል።
ከዚህም በተጨማሪ በኤርትራ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር፣ በቃል አቀባይ፣ በኢትዮጵያ የኤርትራ ኤምባሲ… ወዘተላይ ባደረግነው ዳሰሳ ይህ መረጃ እንደሌለ አረጋግጠናል።
በመቀጠል ኢትዮጵያ ቼክ ያናገራቸው ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ አንድ የኤርትራ ዲፕሎማት መረጃውየተሳሳተ መሆኑን በዛሬው እለት አሳውቀውናል።
ምንጫቸው ያልታወቀ እና ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ባለመቀበል እንዲሁም ለሌሎች ባለማጋራት የሀሰተኛመረጃ ስርጭትን እንከላከል።
ወቅታዊ መረጃዎችን ቀጥታ በኢሜልዎ ለማግኘት ይመዝገቡ
ያቀረቡትን የግል መረጃ በግላዊ መመሪያችን መሠረት እንጠብቃለን::