ስለ ኢትዮጵያ ቼክ

ኢትዮጵያ ቼክ ሰኔ 2020 ዓ.ም የተቋቋመ የመረጃ አጣሪ ተቋም ነው። እአአ ከነሀሴ 2020 ዓ.ም ጀመሮ የኢንተርኒውስ የኢትዮጵያ ፕሮጀክት አካል በመሆን ቆይቷል። በአሁኑ ጊዜ በኬኒያ የተመዘገበ ሲሆን ሙሉ በሙሉ ነጻ የሆነ የባለአደራ ማህበር በመሆን በመስራት ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ ቼክ በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በትግርኛ ሥራዎቹን ለተከታታዮቹ እያቀረበ የሚገኝ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያ ገጾቹ አማካኝነት ከ7 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን መድረስ ችሏል። ኢትዮጵያ ቼክ በአሁኑ ጊዜ የአፍሪካ ፋክትስ ኔትዎርክ አባል ሲሆን የኢንተርናሽናል ፋክትቼኪንግ ኔትዎርክ ፈራሚ ለመሆን አመልክቷል።

ኢትዮጵያ ቼክ በአሁኑ ጊዜ በ3 ዋና ዋና ተግባራት ላይ አትኩሮ ይሰራል። እነሱም: 

  • መረጃ ማጣራት
  • የሚዲያ አጠቃቀም ንቃት ትምህርት መስጠት እና 
  • ስልጠናና የአቅም ግንባታ ስራዎች ናቸው።

ኢትዮጵያ ቼክ ሰኔ 2020 ዓ.ም የተቋቋመ የመረጃ አጣሪ ተቋም ነው። እአአ ከነሀሴ 2020 ዓ.ም ጀመሮ የኢንተርኒውስ የኢትዮጵያ ፕሮጀክት አካል በመሆን ቆይቷል። በአሁኑ ጊዜ በኬኒያ የተመዘገበ ሲሆን ሙሉ በሙሉ ነጻ የሆነ የባለአደራ ማህበር በመሆን በመስራት ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ ቼክ በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በትግርኛ ሥራዎቹን ለተከታታዮቹ እያቀረበ የሚገኝ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያ ገጾቹ አማካኝነት ከ7 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን መድረስ ችሏል። ኢትዮጵያ ቼክ በአሁኑ ጊዜ የአፍሪካ ፋክትስ ኔትዎርክ አባል ሲሆን የኢንተርናሽናል ፋክትቼኪንግ ኔትዎርክ ፈራሚ ለመሆን አመልክቷል።

ኢትዮጵያ ቼክ በአሁኑ ጊዜ በ3 ዋና ዋና ተግባራት ላይ አትኩሮ ይሰራል። እነሱም: 

  • መረጃ ማጣራት
  • የሚዲያ አጠቃቀም ንቃት ትምህርት መስጠት እና 
  • ስልጠናና የአቅም ግንባታ ስራዎች ናቸው።

የኢትዮጵያ ቼክ ህጋዊነት

ኢትዮጵያ ቼክ በህጋዊ መንገድ የተመዘገበ ለትርፍ ያልተቋቋመ የመረጃ አጣሪ ተቋም ነው። ተቋሙም በኬንያ ሪፐብሊክ የሰነዶች መዝገብ ቤት በባለአደራ ማህበርነት በፋይል ቁጥር 2252/D7/3174/MMXXII ተመዝግቧል።

የገለልተኝነት መርሆች

ኢትዮጵያ ቼክ ነጻና ገለልተኛ ሆኖ የሚሰራ የመረጃ አጣሪ ተቋም ነው። ይህን እውን ለማድረግም ባለሙያዎች ተቋሙን ሲቀላቀሉ መርሆቹን የተመለከተ ስልጠና ይሰጣል። የሚከተሉትም ገዥ የገለልተኝነት መርሆቹ ናቸው:

  • የተቋሙ ሰራተኞች ማንኛውንም የፖለቲካ ፓርቲ መደገፍ እና/ወይም ዘመቻ ማድረግ አይችሉም
  • የተቋሙ ሰራተኞች የተቋሙን ንብረቶች በመጠቀም ማንኛውንም የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ቡድን መደግፍ አይችሉም
  •  የተወሰነ የፖለቲካ አካልን ወይም ግለሰብን የሚጠቅም የመረጃ ማጣራት ስራ ለማድረግ ሲባል የእጅ መንሻ በመቀበል ፈጽሞ የተከለከለ ነው 
  • የተቋሙ ሰራተኞች የተወሰነ የፖለቲካ ፓርቲን ወይም ቡድንን ለመደገፍ በፖለቲካ ስብሰባዎች ወይም ዝግጅቶች ላይ መሳተፍ አይፈቀድላቸውም
  • የግል ምልከታን ወይም አድሎን በመረጃ ማጣራት ሂደት ውስጥ መቀላቀል ፈጽሞ የተከለከለ ነው

ማሳሰቢያ: እነዚህ መርሆች ጥሰው በሚገኙ ሰራተኞች ላይ ተገቢው ማጣራት የሚደረግ ሲሆን ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙ እርምጃ የሚወሰድ ይሆናል።

ድጋፍን በተመለከተ

ኢትዮጵያ ቼክ በኬንያ የተመዘገበ የባለአደራ ማህበር ሲሆን ነሀሴ 2020 እስከ ህዳር 2022 ዓ.ም የኢንተርኒውስ የኢትዮጵያ ፕሮጄክቶች አካልሆኖ ቆይቷል። ከታህሳስ 2022 ዓ.ም ጀመሮ እራሱን የቻለ ነጻ ተቋም በመሆን በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። ከታህሳስ 2022 ዓ.ም ጀመሮ ከኢንተርኒውስ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ስራዎቹን በመከውን ላይ የሚገኝ ሲሆን ድጋፉ እስከ ነሀሴ 2023 ዓ.ም የሚቆይ ነው።

ሊጣሩ የሚችሉ መረጃዎችን እንዴት እንመርጣለን?

ኢዮጵያ ቼክ ሊጣሩ የሚችሉ መረጃዎችን የስርጭት መጠናቸውን፣ የሚያደርሱትን ተጽኖ እንዲሁም አንገብጋቢነታቸውን መሠረት በማድረግ ይመርጣል። እንዲሁም ተከታታይነት ያለው የሚዲያ ክትትል በመከውን ሁሉም ድምጾች የሚካተቱበትን አሰራር ይተገብራር።

የእርማትና የቅሬታ ፖሊሲ

ኢትዮጵያ ቼክ እርማቶችን፣ ቅሬታዎችንና ግብረመልሶችን የሚያስተናግድበት ግለጽ አሰራር ያለው ሲሆን  ስህተቶች ከተፈጠሩ ወቅቱን የጠበቀ የማስተካከያ እርምጃ ይወስዳል። ለዚህም “እርማት” በሚል ርዕስ ስህተቶችን የሚያርምና የሚያስተካክል ይዘት ያወጣል። በተጨማሪም ባጋራቸው ይዘቶች ላይ ዝማኔ የሚኖር ከሆነ “አፕዴት” በሚል ርዕስ ስር ጭማሬ ያደረጋል። በመረጃ ማጣራ ስራችን ስህተቶችን ከተመለከቱ በሚከተሉት አድራሻዎቻችን ያሳውቁን:

 ኢሜል: [email protected]

 አጭር መልዕክት: +252974058699

እንዲጣራ የሚፈልጉት መረጃ ወይም ጥቆማ አለዎት? መልእክትዎን ይላኩልን::